Monday, June 17, 2013
 
 
     
ዜና
ማስታወቂያ
  
Minimize

 
     
 ትምህርቶች    
   
 Print   
ድረ ገጾች
 
Minimize
ዜና

  


ማስታወቂያ

  


ዜና

 የደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል የኢ.ኦ.ተ. ቤ/ክ በጥቅምት 12 ቀን 1997 ዓ.ም ወይም እ.ኤ.አ. በ2003 በፈቃደ እግዚአብሔር በወቅቱ የሰሜን አሜሪካ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በነበሩት በብፁዕአቡነ ማትያስ ቡራኬ እና አባታዊ መመሪያ፤ በደብሩ አስተዳዳሪ በመልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ወ/ሰማያት ታታሪነት እንዲሁም ቁጥራቸው ከ20 በማይበልጡ ነገር ግን ፍቅረ እግዚአብሔር በልቦናቸው በተሳለ ቀና ካህናትእና ምዕመናን አማካይነት በሲያትል ዋሽንግተን ተመሰርቶ አገልግሎቱን በተለያዩ የኪራይ ቤቶች ሲፈጽም ቆይቶ እንደ እግዚአብሄር ፈቃድ በጥር 4/2003 /Jan. 12/2011/ የእራሱን ህንጻ ቤተክርስቲያን ሊገዛ ችሏል::

የተገዛው ህንጻ በ ጥር 29/2003 /Feb. 06/2011/ ለአገልግሎት ምቹ ሆኖ ከተዘጋጀ በኋላ አገልግሎት መስጠት ጀምሮ በ ሐምሌ 10/2003 / ጁላይ 17/2011/ በደመቀ ሁኔታ የምርቃት በዓሉ ተከብሮ ውሏል::

  ተጨማሪ ያንብቡ


ማስታወቂያ

"ኑ፣ በእግዚአብሔር ደስ ይበለን ለአምላክ ለመድኃኒታችን እልል እንበል::"  መዝ 95፣1

ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን በሙሉ::

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ምዕራብ አሜሪካና ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኘው የደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በእግዚአብሔር ቸርነት በሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት እንዲሁም በሲያትልና አካባቢው ሕዝበ ክርስቲያን ጥረት ንብረትነቱን የኢትዮጵያ  ኦ ርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክን በቅርቡ በኤድመንድ ዋሽንግተን ላይ ገዝቷል:: ይህንኑ ቤተ ክርስቲያን ከፍ ባለ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት በብጹዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና ጸሎት ቅዳሜ ሓምሌ 10 ቀን 2003 ዓ ም / July 16 & 17, 2011/ያስመርቃል::

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

በየዓመቱ ሰኔ 12 የሚከበረው የቅዱስ ሚካዔል የመታሰቢያ በዓል በሲያትል ደብረ ሠላም ቅዱስ ሚካዔል ቤተክርስቲያን በደመቀ ሁኔታ ተከብሮ ዋለ:: በበዓሉ ላይ የሃገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ እንዲሁም ከተለያዩ ስቴቶች የመጡ አባቶች ካህናት እና ምእመናን ተገኝተዋል::

በዓሉ ቅዳሜ በዋዜማ ቁመት ተጀምሮ፣ ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ በማህሌት እና በመዝሙር በመቀጠል፣ እሁድ ዕለት በደመቀ ሁኔታ በቅዳሴ፣ በመዝሙር እና በትምህርት ተከብሮ ውሏል::

የዚህን ዓመት ክብረ በዓል ልዩ የሚያደርገው በአዲሱ ህንጻ ቤተ ክርስቲያን መከበሩ እና በበዓሉ ላይ እጅግ ብዙ አባቶች እና መእመናን ከአጥቢያውና ከተለያዩ ስቴቶች በመሰባሰብ በቤተ ክርስቲያኑ ቅጽረ ግቢ በዑደት በደመቀ ሁኔታ መከበሩ ነው::

የበዓሉን አከባበር በፎቶ ለማየት ይህንን የጫኑ::

  


Page 1 of 3First   Previous   [1]  2  3  Next   Last   

      
   
 Print   
      
   
 Print   
  
Minimize
   ለአባላት Minimize  
  
Copyright 2009 by DSK Michael  Terms Of Use  Privacy Statement